1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ሪያል ማድሪድ ባዬርን ሙይንሽንን አሸነፈ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 30 2016

በሻምፒዮንስ ሊግ የደርሶ መልስ የግማሽ ፍጻሜ ግጥሚያ ዛሬ ማታ የጀርመኑ ባዬርን ሙይንሽን በስፔኑ ሪያል ማድሪድ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች 2 ለ1 ተሸነፈ ። እስከ 88ኛው ደቂቃ ድረስ ባዬርን ሙይንሽን ሪያል ማድሪድን 1 ለ 0 እየመራ ነበር ። በደርሶ መልስ ውጤት ሪያል ማድሪድ 4 ለ3 አሸንፎ ለፍጻሜ አልፏል ።

https://p.dw.com/p/4feRk
Champions League Halbfinale  Real Madrid vs Bayern München
ምስል Susana Vera/REUTERS

በሻምፒዮንስ ሊግ የደርሶ መልስ የግማሽ ፍጻሜ ግጥሚያ ዛሬ ማታ የጀርመኑ ባዬርን ሙይንሽን በስፔኑ ሪያል ማድሪድ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች 2 ለ1 ተሸነፈ ። እስከ 88ኛው ደቂቃ ድረስ ባዬርን ሙይንሽን ሪያል ማድሪድን 1 ለ 0 እየመራ ነበር ። በደርሶ መልስ ውጤት ሪያል ማድሪድ 4 ለ3 አሸንፎ ለፍጻሜ አልፏል ። ለባዬርን ሙይንሽ በ68ኛው ደቂቃ ካናዳዊው አልፎንሶ ዳቪስ በድንቅ ኹኔታ ኳሷን ከመረብ ቢያሳርፍም፤ ተቀይሮ የገባው የ34 ዓመቱ አጥቂ  ሆሴሉ 88 እና 91ኛው ደቂቃ ላይ ለሪያል ማድሪድ አስቆጥሯል ። 

ትናንት በነበረው ጨዋታ ሌላኛው የጀርመን ቡድን ቦሩስያ ዶርትሙንድ የፈረንሣዩ ፓሪ ሳን ጃርሞን 1 ለ0 አሸንፏል ። በደርሶ መልስ የ2 ለ0 ውጤትቱም ቦሩስያ ዶርትሙንድ እንግሊዝ ዌብሌይ ስታዲየም ውስጥ ግንቦት 24 ለሚካሄደው የፍጻሜ ውድድር ማለፉን አረጋግጧል ። ባዬርን ሙይንሽን በሜዳው አሊያንትስ አሬና ስታዲየም ባደረገው ግጥሚያ የተለያየው በሁለት እኩል ውጤት ነበር ። ዛሬ ማታ ሪያል ማድሪድ በሜዳው ሳንቲያጎ ቤርናቤዉ  ባዬርን ሙይንሽንን ድል በማድረጉ በፍጻሜው ቦሩስያ ዶርትሙንድን ይገጥማል ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር