የአሸባሪነት ተጠርጣሪዎችና የአይን ምስክሮች
ማክሰኞ፣ ሰኔ 23 2001ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነትና በነብሰ-ገዳይነት ጥርጣሬ ባሰራቸዉ የቀድሞ የጦር መኮንኖችና ሲቢሎች ላይ የተቆጠሩ የአይን ምሥክሮች ዛሬ ቃላቸዉን ለፍርድ ቤት መስጠት ጀመሩ።አቃቤ-ሕግ ሕገ-መንግሥታዊዉን ሥርዓት ለማሸበርና ባለሥልጣናትን ለመግደል በግንቦት ሰባት የፖለቲካ ማሕበር ሥም ተደራጅተዋል የሚል ክስ በመሰረተባቸዉ ተጠርጣሪዎች ላይ ከዘጠና የሚበልጡ ምስክሮችን ቆጥሯል።ዛሬ አዲስ አበባ ላስቻለዉ ክፍተኛ ፍርድ ቤት ቃላቸዉን የሰጡት ምስክሮች ግን ከተከሳሾቹ መካካል የተወሰኑት ቤት ሲፈተሽ በታዛቢነት የተገኙ ናቸዉ።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ታደሰ እንግዳዉ የፍርድ ቤቱን ዉሎ ተከታትሎታል።
ታደሰ እንግዳዉ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ